92 - The Night - Al-Layl
:1
በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
:2
በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡
:3
ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡
:4
ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡
:5
የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡
:6
በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤
:7
ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
:8
የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤
:9
በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤
:10
ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
:11
በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
:12
ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡
:13
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡
:14
የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡
:15
ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡
:16
ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡
:17
አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡
:18
ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡
:19
ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡
:20
ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡
:21
ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡