91 - The Sun - Ash-Shams
:1
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
:2
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
:3
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
:4
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
:5
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
:6
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
:7
በነፍስም ባስተካከላትም፤
:8
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
:9
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
:10
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
:11
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
:12
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
:13
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
:14
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
:15
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡