ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

90 - The City - Al-Balad

:1

በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡

:2

አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን፡፡

:3

በወላጂም በወለዳቸውም ሰዎች (በአዳምና በዘሮቹ ሁሉ እምላለሁ)፡፡

:4

ሰውን ሁሉ በእርግጥ በልፋት ውስጥ ኾኖ ፈጠርነው፡፡

:5

በእርሱ ላይ አንድም የማይችል መኾኑን ይጠረጥራልን?

:6

«ብዙን ገንዘብ አጠፋሁ» ይላል፡፡

:7

አንድም ያላየው መኾኑን ያስባልን?

:8

ለእርሱ ሁለት ዓይኖችን አላደረግንለትምን?

:9

ምላስንና ሁለት ከንፈሮችንም፡፡

:10

ሁለትን መንገዶችም አልመራነውምን?

:11

ዓቀበቲቱንም አልወጣም፡፡

:12

ዓቀበቲቱም (መውጣቷ) ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?

:13

(እርሱ) ጫንቃን መልቀቅ ነው፡፡

:14

ወይም የረኃብ ባለቤት በኾነ ቀን ማብላት፡፡

:15

የዝምድና ባለቤት የኾነን የቲም፤

:16

ወይም የዐፈር ባለቤት የኾነን ድኻ (ማብላት ነው)፡፡

:17

(ዐቀበቲቱን አልወጣም)፡፡ ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡

:18

እነዚያ (ይህንን የፈጸሙ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡

:19

እነዚያም በአንቀጾቻችን የካዱት እነርሱ የግራ ጓዶች ናቸው፡፡

:20

በእነርሱ ላይ የተዘጋች እሳት አልለች፡፡