ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

89 - The Dawn - Al-Fajr

:1

በጎህ እምላለሁ፡፡

:2

በዐሥር ሌሊቶችም፡፡

:3

በጥንዱም በነጠላውም፡፡

:4

በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡

:5

በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?

:6

ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?

:7

በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡

:8

በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡

:9

በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡

:10

በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡

:11

በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡

:12

በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)

:13

በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡

:14

ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡

:15

ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡

:16

በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡

:17

ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡

:18

ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡

:19

የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡

:20

ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡

:21

ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤

:22

መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ለሱ ክብር በምስማማ መልኩ) በመጣ ጊዜ፤

:23

ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?

:24

«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡

:25

በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡

:26

የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡

:27

(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!

:28

«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡

:29

«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡

:30

ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡