88 - The Overwhelming - Al-Ghāshiyah
:1
የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን?
:2
ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡
:3
ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡
:4
ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡
:5
በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡
:6
ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡
:7
የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡
:8
ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡
:9
ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡
:10
በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡
:11
በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም፡፡
:12
በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አልሉ፡፡
:13
በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡
:14
በተርታ የተኖሩ ብርጭቆዎችም፡፡
:15
የተደረደሩ መከዳዎችም፡፡
:16
የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አልሉ)፡፡
:17
(ከሓዲዎች) አይመለከቱምን? ወደ ግመል እንዴት እነደተፈጠረች!
:18
ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች!
:19
ወደ ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!
:20
ወደ ምድርም እንዴ እንደተዘረጋች (አይመለከቱምን?)
:21
አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና፡፡
:22
በእነርሱ ላይ ተሿሚ (አስገዳጅ) አይደለህም፡፡
:23
ግን (ከእውነት) የዞረና የካደ ሰው፤
:24
አላህ ታላቁን ቅጣት ይቀጣዋል፡፡
:25
መመለሻቸው ወደእኛ ብቻ ነው፡፡
:26
ከዚያም ምርመራቸው በእኛ ላይ ብቻ ነው፡፡