ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

88 - The Overwhelming - Al-Ghāshiyah

:1

የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን?

:2

ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡

:3

ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡

:4

ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡

:5

በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡

:6

ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡

:7

የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡

:8

ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡

:9

ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡

:10

በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡

:11

በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም፡፡

:12

በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አልሉ፡፡

:13

በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡

:14

በተርታ የተኖሩ ብርጭቆዎችም፡፡

:15

የተደረደሩ መከዳዎችም፡፡

:16

የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አልሉ)፡፡

:17

(ከሓዲዎች) አይመለከቱምን? ወደ ግመል እንዴት እነደተፈጠረች!

:18

ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች!

:19

ወደ ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!

:20

ወደ ምድርም እንዴ እንደተዘረጋች (አይመለከቱምን?)

:21

አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና፡፡

:22

በእነርሱ ላይ ተሿሚ (አስገዳጅ) አይደለህም፡፡

:23

ግን (ከእውነት) የዞረና የካደ ሰው፤

:24

አላህ ታላቁን ቅጣት ይቀጣዋል፡፡

:25

መመለሻቸው ወደእኛ ብቻ ነው፡፡

:26

ከዚያም ምርመራቸው በእኛ ላይ ብቻ ነው፡፡