ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት
1

በል «በሰዎች ፈጣሪ እጠበቃለሁ፡፡

2

«የሰዎች ሁሉ ንጉሥ በኾነው፡፡

3

«የሰዎች አምላክ በኾነው፡፡

4

«ብቅ እልም ባይ ከኾነው ጎትጓች (ሰይጣን) ክፋት፡፡

5

«ከዚያ በሰዎች ልቦች ውስጥ የሚጎተጉት ከኾነው፡፡

6

«ከጋኔኖችም ከሰዎችም (ሰይጣናት እጠበቃለሁ በል)፡፡»