ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

87 - The Most High - Al-'A`lá

:1

ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡

:2

የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡

:3

የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡

:4

የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡

:5

(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡

:6

(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡

:7

አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡

:8

ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡

:9

ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡

:10

(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡

:11

መናጢውም ይርቃታል፡፡

:12

ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡

:13

ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡

:14

የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡

:15

የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡

:16

ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡

:17

መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡

:18

ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡

:19

በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡