ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

86 - The Nightcommer - Aţ-Ţāriq

:1

በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡

:2

የሌሊት መጪውም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

:3

ጨለማን ቀዳጁ ኮከብ ነው፡፡

:4

ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡

:5

ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፡፡

:6

ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ፡፡

:7

ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ)፡፡

:8

እርሱ (አላህ) በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡

:9

ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን፡፡

:10

ለእርሱም (ለሰው) ኀይልና ረዳት ምንም የለውም፡፡

:11

የመመለስ ባለቤት በኾነችው ሰማይም እምላለሁ፡፡

:12

(በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በኾነችው ምድርም፤

:13

እርሱ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ ቃል ነው፡፡

:14

እርሱም ቀልድ አይደለም፡፡

:15

እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ይሠራሉ፡፡

:16

(እኔ) ተንኮልንም እመልሳለሁ፡፡

:17

ከሓዲዎችንም ቀን ስጣቸው፡፡ ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው፡፡