ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

85 - The Mansions of the Stars - Al-Burūj

:1

የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡

:2

በተቀጠረው ቀንም፤

:3

በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡

:4

የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡

:5

የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡

:6

እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡

:7

እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡

:8

ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡

:9

በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡

:10

እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡

:11

እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡

:12

የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡

:13

እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡

:14

እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡

:15

የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡

:16

የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡

:17

የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?

:18

የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡

:19

በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡

:20

አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡

:21

ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡

:22

የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡