ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

84 - The Sundering - Al-'Inshiqāq

:1

ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤

:2

ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤

:3

ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤

:4

በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤

:5

ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡

:6

አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡

:7

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤

:8

በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡

:9

ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡

:10

መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤

:11

(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡

:12

የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡

:13

እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡

:14

እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡

:15

አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡

:16

አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡

:17

በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤

:18

በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡

:19

ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡

:20

የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?

:21

በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)

:22

በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡

:23

አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡

:24

በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡

:25

ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡