ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

83 - The Defrauding - Al-Muţaffifīn

:1

ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡

:2

ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡

:3

ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡

:4

እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?

:5

በታላቁ ቀን፡፡

:6

ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡

:7

በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡

:8

ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

:9

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

:10

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:11

ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡

:12

በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡

:13

አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

:14

ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡

:15

ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡

:16

ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡

:17

ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡

:18

በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡

:19

ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

:20

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

:21

ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡

:22

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡

:23

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡

:24

በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡

:25

ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡

:26

ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡

:27

መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡

:28

ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡

:29

እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡

:30

በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡

:31

ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡

:32

ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡

:33

በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡

:34

ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡

:35

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡

:36

ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡