ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

82 - The Cleaving - Al-'Infiţār

:1

ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤

:2

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤

:3

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤

:4

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤

:5

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡

:6

አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?

:7

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡

:8

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡

:9

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡

:10

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤

:11

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡

:12

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡

:13

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡

:14

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡

:15

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡

:16

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡

:17

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

:18

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

:19

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡