81 - The Overthrowing - At-Takwīr
:1
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
:2
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
:3
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
:4
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
:5
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
:6
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
:7
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
:8
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
:9
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
:10
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
:11
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
:12
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
:13
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
:14
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
:15
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
:16
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
:17
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
:18
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
:19
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
:20
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
:21
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
:22
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
:23
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
:24
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
:25
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
:26
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
:27
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
:28
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
:29
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡