ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

93 - The Morning Hours - Ađ-Đuĥaá

:1

በረፋዱ እምላለሁ፡፡

:2

በሌሊቱም ጸጥ ባለ ጊዜ፤

:3

ጌታህ አላሰናበተህም፤ አልጠላህምም፡፡

:4

መጨረሻይቱም (ዓለም) ከመጀመሪያይቱ ይልቅ ላንተ በላጭ ናት፡፡

:5

ጌታህም ወደ ፊት (ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል፡፡ ትደሰታለህም፡፡

:6

የቲም ኾነህ አላገኘህምና አላስጠጋህምን? (አስጠግቶሃል)፡፡

:7

የሳትክም ኾነህ አገኘህ መራህም፡፡

:8

ድኻም ኾነህ አገኘህ፤ አከበረህም፡፡

:9

የቲምንማ አትጨቁን፡፡

:10

ለማኝንም አትገላምጥ፡፡

:11

በጌታህም ጸጋ አውራ፤ (ግለጻት)፡፡