93 - The Morning Hours - Ađ-Đuĥaá
:1
በረፋዱ እምላለሁ፡፡
:2
በሌሊቱም ጸጥ ባለ ጊዜ፤
:3
ጌታህ አላሰናበተህም፤ አልጠላህምም፡፡
:4
መጨረሻይቱም (ዓለም) ከመጀመሪያይቱ ይልቅ ላንተ በላጭ ናት፡፡
:5
ጌታህም ወደ ፊት (ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል፡፡ ትደሰታለህም፡፡
:6
የቲም ኾነህ አላገኘህምና አላስጠጋህምን? (አስጠግቶሃል)፡፡
:7
የሳትክም ኾነህ አገኘህ መራህም፡፡
:8
ድኻም ኾነህ አገኘህ፤ አከበረህም፡፡
:9
የቲምንማ አትጨቁን፡፡
:10
ለማኝንም አትገላምጥ፡፡
:11
በጌታህም ጸጋ አውራ፤ (ግለጻት)፡፡