ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

78 - The Tidings - An-Naba

:1

ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?

:2

ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡

:3

ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡

:4

ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

:5

ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡

:6

ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?

:7

ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?

:8

ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡

:9

እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡

:10

ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡

:11

ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡

:12

ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡

:13

አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡

:14

ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡

:15

በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡

:16

የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡

:17

የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡

:18

በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡

:19

ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡

:20

ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡

:21

ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡

:22

ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡

:23

በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤

:24

በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡

:25

ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡

:26

ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡

:27

እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡

:28

በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡

:29

ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡

:30

ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡

:31

ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡

:32

አትክልቶችና ወይኖችም፡፡

:33

እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡

:34

የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡

:35

በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡

:36

ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡

:37

የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡

:38

መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡

:39

ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡

:40

እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡