ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

77 - The Emissaries - Al-Mursalāt

:1

ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

:2

በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

:3

መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

:4

መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

:5

መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

:6

ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

:7

ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

:8

ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

:9

ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

:10

ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

:11

መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡

:12

ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤

:13

ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

:14

የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

:15

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:16

የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?

:17

ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡

:18

በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

:19

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:20

ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?

:21

በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡

:22

እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም

:23

መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!

:24

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:25

ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?

:26

ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

:27

በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡

:28

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:29

«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

:30

«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

:31

አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡

:32

እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡

:33

(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡

:34

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:35

ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡

:36

ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡

:37

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:38

ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

:39

ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡

:40

ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:41

ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

:42

ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

:43

«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

:44

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

:45

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:46

ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡

:47

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:48

«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡

:49

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

:50

ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?