ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት
1

እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡

2

(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤

3

በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤

4

በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤

5

በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡

6

ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡

7

እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡

8

እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡

9

(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤

10

በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡

11

ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡