ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

100 - The Courser - Al-`Ādiyāt

:1

እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡

:2

(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤

:3

በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤

:4

በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤

:5

በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡

:6

ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡

:7

እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡

:8

እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡

:9

(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤

:10

በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡

:11

ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡