1
እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
2
(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
3
በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
4
በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
5
በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
6
ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡
7
እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
8
እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
9
(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤
10
በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡
11
ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡