100 - The Courser - Al-`Ādiyāt
:1
እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
:2
(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
:3
በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
:4
በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
:5
በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
:6
ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡
:7
እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
:8
እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
:9
(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤
:10
በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡
:11
ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡