ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

99 - The Earthquake - Az-Zalzalah

:1

ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤

:2

ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤

:3

ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤

:4

በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡

:5

ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡

:6

በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡

:7

የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

:8

የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡