99 - The Earthquake - Az-Zalzalah
:1
ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤
:2
ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤
:3
ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤
:4
በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡
:5
ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡
:6
በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡
:7
የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡
:8
የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡