ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት
1

ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤

2

ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤

3

ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤

4

በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡

5

ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡

6

በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡

7

የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

8

የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡