99 - The Earthquake - Az-Zalzalah
1
ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤
2
ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤
3
ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤
4
በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡
5
ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡
6
በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡
7
የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡
8
የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡