ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

96 - The Clot - Al-`Alaq

:1

አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡

:2

ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡

:3

አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤

:4

ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡

:5

ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡

:6

በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡

:7

ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡

:8

መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

:9

አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡

:10

ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤

:11

አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤

:12

ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤

:13

አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤

:14

አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?

:15

ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡

:16

ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡

:17

ሸንጎውንም ይጥራ፡፡

:18

(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡

:19

ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡