ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

95 - The Fig - At-Tīn

:1

በበለስና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡

:2

በሲኒን ተራራም፤

:3

በዚህ በጸጥተኛው አገርም (እምላለሁ)፡፡

:4

ሰውን በጣም በአማረ አቋም ላይ ፈጠርነው፡፡

:5

ከዚያም (ከፊሉን) ከዝቅተኞች ሁሉ በታች አድርገን መለስነው፡፡

:6

ግን እነዚያ ያመኑት መልካሞችንም የሠሩት ለእነርሱ ተቆራጭ ያልኾነ ምንዳ አልላቸው፡፡

:7

ታዲያ ከዚህ በኋላ በፍርዱ ምን አስተባባይ አደረገህ?

:8

አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን? (ነው)፡፡