ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት
1

በበለስና በዘይት ወይራ እምላለሁ፡፡

2

በሲኒን ተራራም፤

3

በዚህ በጸጥተኛው አገርም (እምላለሁ)፡፡

4

ሰውን በጣም በአማረ አቋም ላይ ፈጠርነው፡፡

5

ከዚያም (ከፊሉን) ከዝቅተኞች ሁሉ በታች አድርገን መለስነው፡፡

6

ግን እነዚያ ያመኑት መልካሞችንም የሠሩት ለእነርሱ ተቆራጭ ያልኾነ ምንዳ አልላቸው፡፡

7

ታዲያ ከዚህ በኋላ በፍርዱ ምን አስተባባይ አደረገህ?

8

አላህ ከፈራጆች ሁሉ ይበልጥ ፈራጅ አይደለምን? (ነው)፡፡