ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

55 - The Beneficent - Ar-Raĥmān

:1

አል-ረሕማን፤

:2

ቁርኣንን አስተማረ፡፡

:3

ሰውን ፈጠረ፡፡

:4

መናገርን አስተማረው፡፡

:5

ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡

:6

ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡

:7

ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡

:8

በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡

:9

መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡

:10

ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡

:11

በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡

:12

የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡

:13

(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:14

ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡

:15

ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡

:16

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:17

የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡

:18

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:19

ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡

:20

(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡

:21

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›

:22

ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡

:23

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:24

እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡

:25

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:26

በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡

:27

የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡

:28

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:29

በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡

:30

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›

:31

እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡

:32

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:33

የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)

:34

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:35

በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡

:36

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:37

ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡

:38

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:39

በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡

:40

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:41

ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡

:42

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡

:43

ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡

:44

በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡

:45

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:46

በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡

:47

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:48

የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡

:49

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:50

በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡

:51

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:52

በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡

:53

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:54

የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡

:55

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:56

በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡

:57

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:58

ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡

:59

ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:60

የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?

:61

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:62

ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡

:63

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›

:64

ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡

:65

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:66

በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡

:67

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:68

በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡

:69

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:70

በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡

:71

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:72

በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡

:73

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:74

ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡

:75

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?

:76

በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡

:77

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

:78

የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡