ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

104 - The Traducer - Al-Humazah

:1

ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡

:2

ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ ፤(ወዮለት)፡፡

:3

ገንዘቡ የሚያዘወትረው መኾኑን ያስባል፡፡

:4

ይከልከል፤ በሰባሪይቱ (እሳት) ውስጥ በእርግጥ ይጣላል፡፡

:5

ሰባሪይቱም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?

:6

የተነደደችው የአላህ እሳት ናት፡፡

:7

ያቺ በልቦች ላይ የምትዘልቅ የኾነችው፡፡

:8

እርሷ በእርግጥ በእነርሱ ላይ የተዘጋጀች ናት፡፡

:9

በተዘረጋች አዕማድ ውስጥ (የተዘጋች ናት)፡፡