104 - The Traducer - Al-Humazah
:1
ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡
:2
ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ ፤(ወዮለት)፡፡
:3
ገንዘቡ የሚያዘወትረው መኾኑን ያስባል፡፡
:4
ይከልከል፤ በሰባሪይቱ (እሳት) ውስጥ በእርግጥ ይጣላል፡፡
:5
ሰባሪይቱም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
:6
የተነደደችው የአላህ እሳት ናት፡፡
:7
ያቺ በልቦች ላይ የምትዘልቅ የኾነችው፡፡
:8
እርሷ በእርግጥ በእነርሱ ላይ የተዘጋጀች ናት፡፡
:9
በተዘረጋች አዕማድ ውስጥ (የተዘጋች ናት)፡፡