104 - The Traducer - Al-Humazah
1
ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡
2
ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ ፤(ወዮለት)፡፡
3
ገንዘቡ የሚያዘወትረው መኾኑን ያስባል፡፡
4
ይከልከል፤ በሰባሪይቱ (እሳት) ውስጥ በእርግጥ ይጣላል፡፡
5
ሰባሪይቱም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
6
የተነደደችው የአላህ እሳት ናት፡፡
7
ያቺ በልቦች ላይ የምትዘልቅ የኾነችው፡፡
8
እርሷ በእርግጥ በእነርሱ ላይ የተዘጋጀች ናት፡፡
9
በተዘረጋች አዕማድ ውስጥ (የተዘጋች ናት)፡፡