All Islam Directory
1

ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡

2

ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ ፤(ወዮለት)፡፡

3

ገንዘቡ የሚያዘወትረው መኾኑን ያስባል፡፡

4

ይከልከል፤ በሰባሪይቱ (እሳት) ውስጥ በእርግጥ ይጣላል፡፡

5

ሰባሪይቱም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?

6

የተነደደችው የአላህ እሳት ናት፡፡

7

ያቺ በልቦች ላይ የምትዘልቅ የኾነችው፡፡

8

እርሷ በእርግጥ በእነርሱ ላይ የተዘጋጀች ናት፡፡

9

በተዘረጋች አዕማድ ውስጥ (የተዘጋች ናት)፡፡