ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት

75 - The Resurrection - Al-Qiyāmah

:1

(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡

:2

(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

:3

ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?

:4

አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡

:5

ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡

:6

«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡

:7

ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡

:8

ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡

:9

ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡

:10

«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡

:11

ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡

:12

በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

:13

ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡

:14

በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡

:15

ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡

:16

በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡

:17

(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡

:18

ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡

:19

ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡

:20

(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡

:21

መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡

:22

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡

:23

ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡

:24

ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡

:25

በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡

:26

ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤

:27

«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡

:28

(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡

:29

ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡

:30

በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡

:31

አላመነምም አልሰገደምም፡፡

:32

ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡

:33

ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡

:34

የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡

:35

ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡

:36

ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?

:37

የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?

:38

ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡

:39

ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡

:40

ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?