All Islam Directory
1

መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡

2

መገሠጽንም በሚገሥጹት፤

3

ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡

4

አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡

5

የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡

6

እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡

7

አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡

8

ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡

9

የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡

10

ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡

11

ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡

12

ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡

13

በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡

14

ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡

15

ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

16

«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?

17

«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡

18

«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡

19

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡

20

«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡

21

«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡

22

(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡

23

«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡

24

«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡

25

(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡

26

በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡

27

የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡

28

(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡

29

(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡

30

«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡

31

«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡

32

«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡

33

ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡

34

እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

35

እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡

36

እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡

37

አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡

38

እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡

39

ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡

40

ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡

41

እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡

42

ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤

43

በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡

44

ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡

45

ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡

46

ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡

47

በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡

48

እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡

49

እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡

50

የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡

51

ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡

52

«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡

53

«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡

54

እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡

55

ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡

56

ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡

57

«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»

58

(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?

59

«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡

60

ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡

61

ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡

62

በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?

63

እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡

64

እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡

65

እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡

66

እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡

67

ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡

68

ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡

69

እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡

70

እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡

71

ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡

72

በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡

73

የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡

74

ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

75

ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!

76

እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡

77

ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤

78

በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡

79

«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»

80

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

81

እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡

82

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

83

ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡

84

ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡

85

«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡

86

«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?

87

«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡

88

በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡

89

«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡

90

ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡

91

ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»

92

«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»

93

በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡

94

ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡

95

አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»

96

«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»

97

«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡

98

በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡

99

አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»

100

ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡

101

ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡

102

ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡

103

ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡

104

ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!

105

ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

106

ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡

107

በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡

108

በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡

109

ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡

110

እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

111

እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡

112

በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡

113

በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡

114

በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡

115

እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡

116

ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡

117

በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡

118

ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡

119

በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡

120

ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡

121

እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

122

ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡

123

ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

124

ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?

125

በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?

126

አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?

127

አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡

128

ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

129

በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡

130

ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡

131

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

132

እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡

133

ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

134

እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡

135

(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡

136

ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡

137

እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡

138

በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?

139

ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

140

ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡

141

ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡

142

እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡

143

እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤

144

እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡

145

እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡

146

በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡

147

ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡

148

አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡

149

(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»

150

ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?

151

ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-

152

«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡

153

በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?

154

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!

155

አትገነዘቡምን?

156

ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?

157

«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡

158

በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡

159

አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡

160

ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡

161

እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤

162

በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡

163

ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡

164

(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡

165

እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡

166

እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡

167

እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-

168

«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤

169

«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»

170

ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

171

(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡

172

እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

173

ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

174

ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡

175

እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡

176

በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?

177

በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!

178

እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡

179

ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡

180

የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡

181

በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤

182

ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡