ሁሉም የእስልምና ቤተ መጻሕፍት
1

ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡

2

ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡

3

አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡

4

ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡

5

ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡

6

በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡

7

ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡

8

በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

9

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡

10

ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡

11

«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡

12

(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡

13

«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡

14

«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»

15

(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡

16

«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡

17

«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»

18

(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን

19

«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡

20

(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡

21

«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡

22

«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»

23

ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»

24

(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡

25

(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡

26

(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡

27

(ፈርዖን)

28

(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡

29

(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡

30

(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡

31

«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡

32

በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡

33

እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡

34

(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡

35

«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡

36

አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡

37

«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»

38

ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡

39

ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡

40

«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡

41

«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡

42

«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡

43

ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡

44

ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡

45

ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡

46

ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡

47

(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡

48

«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»

49

(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡

50

(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡

51

«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»

52

ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡

53

ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡

54

«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡

55

«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡

56

«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡

57

አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡

58

ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡

59

እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡

60

ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡

61

ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡

62

(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡

63

ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡

64

እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡

65

ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡

66

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

67

በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

68

ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

69

በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡

70

ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡

71

«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡

72

(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን

73

«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»

74

«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡

75

«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን

76

«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»

77

«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡

78

«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡

79

«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡

80

«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡

81

«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡

82

ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡

83

ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡

84

በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡

85

የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡

86

ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡

87

በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡

88

ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡

89

ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»

90

ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡

91

ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡

92

ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»

93

«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»

94

በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡

95

የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡

96

እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-

97

በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡

98

(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡

99

አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡

100

ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡

101

አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡

102

ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡

103

በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

104

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

105

የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡

106

ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን

107

«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

108

«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡

109

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

110

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»

111

(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡

112

(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡

113

«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡

114

«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡

115

«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»

116

«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡

117

(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡

118

«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»

119

እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡

120

ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡

121

በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡

122

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

123

ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡

124

ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን

125

«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

126

«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡

127

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

128

«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን

129

«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን

130

«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን

131

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

132

«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡

133

«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡

134

«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡

135

«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»

136

(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡

137

«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

138

«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡

139

አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡

140

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

141

ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡

142

ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን

143

«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

144

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

145

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

146

«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን

147

«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡

148

«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)

149

«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡

150

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

151

«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡

152

«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»

153

(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡

154

«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»

155

(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡

156

«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»

157

ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡

158

ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡

159

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

160

የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡

161

ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን

162

«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

163

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

164

«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

165

«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን

166

«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»

167

(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»

168

(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡

169

«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»

170

እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡

171

በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡

172

ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡

173

በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡

174

በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡

175

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

176

የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤

177

ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን

178

«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡

179

«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡

180

«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡

181

«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡

182

«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡

183

«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡

184

«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»

185

አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡

186

«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡

187

«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»

188

«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡

189

አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡

190

በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡

191

ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡

192

እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡

193

እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤

194

ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡

195

ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡

196

እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡

197

የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን

198

ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤

199

በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡

200

እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡

201

አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡

202

እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡

203

(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡

204

በቅጣታችን ያቻኩላሉን

205

አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤

206

ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤

207

ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡

208

አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡

209

(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡

210

ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡

211

ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡

212

እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡

213

ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡

214

ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡

215

ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡

216

«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡

217

አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡

218

በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡

219

በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡

220

እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡

221

ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን

222

በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡

223

የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡

224

ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡

225

እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን

226

እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤

227

እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡